የአዊ ብሄረሰብ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በብሄረሰብ ዞኑ ዋና ከተማ በሆነችው በእንጅባራ ከተማ የሚገኝ ሲሆን ከ1986 ጀምሮ ለዞኑ ህብረተሰብ ህግን መሠረት ያደረገ የዳኝነት ውሣኔ በመስጠት ለዞኑ ኢኮኖሚ ዕድገት ለመልካም አስተዳደርና ዴሞክራሲ ምስረታ ሠላምና መረጋጋት መስፈን የበኩሉን አስተዎፅኦ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡
ፍ/ቤቶችን የበለጠ ተደራሽ ቀልጣፋ ለማድረግ የአገልገሎት ፈላጊዎችን እርካታ ለማረጋገጥ ከፍተኛ ፍ/ቤቱ በስሩም ባሉ 7 የወረዳ ፍ/ቤቶች እና በ 2 ንዑስ ወረዳ ፍ/ቤቶች እንዲሁም በአንድ የከፍተኛ ሸርያ እና በ 2 የወረዳ ሸርያ ፍ/ቤት አደረጃጀት መዋቅር በመዘርጋት |
|
አቶ አስፋው አረጋ
የአዊ ዞን ከፍተና ፍ/ቤት ፕሬዘዳንት
ተጨማሪ መረጃ > |
ከፍ/ፍ/ቤቱ ወረዳ ፍ/ቤቶችን ጨምሮ 355 ሠራተኞች ሲኖሩ ከነዚህ ውስጥም 47 ወንዶች 20 ሴቶች በድምሩ 67 ዳኞች ፣ወንድ 2 ወንድ የህግ ኦፊሰር 3 ወንድ የሸሪያ ፍ/ቤት ዳኞች እና 1 ወንድ ተከላካይ ጠበቃ የሚገኙ ሲሆን በተጨማሪ ድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች ደግሞ 159 ወንዶች እና 123 ሴቶች በድምሩ 282 ናቸው፡፡
በመሆኑም ፍ/ቤቶችን የበለጠ ተደራሽ ቀልጣፋ ለማድረግም የአገልግሎት ፈላጊዎችን እርካታ ለማረጋገጥ ከፍ/ፍ/ቤቱ በ3 ዋና ሂደትና በ7 ደጋፊ የሥራ ሂደት እንዲሁም ወረዳ ፍ/ቤቶች ደግሞ በ 2 ዋና የሥራ ሂደትና በ 5 ደጋፊ የሥራ ሂደት ጥናቶች ተጠናቀው ወደ ትግበራ በመግባት የዘመኑን ቴክኖሎጅ በመጠቀም ዘመናዊ የአሰራር ዘዴ በማደራጀት የሰው ኃይሉንና ተቋማዊ ብቃቱን ከመቼውም ጊዜ የተሻለና የተሳለጠ አሰራር በማጐለበት ላይ ይገኛልሉ፡፡
|